የቱሪስት መስዕህብ፤ ብዙ አማራጮች ያላት!
ለምን ጎንደር?
ጎንደር ከተማ የቱሪስት መስዕህብ ያሉባት ከተማ መሆና ጋር ተያያዞ ጥሩ የገበያ ዕድል ያላት ከተማ መሆና፣ የተሻለ የመሰረተ ልማት ማለትም የየብስ እና የአየር ትራንስፖርት፣ የውሃ አቅርቦት፣ የደረቅ ወደብ ተጠቃሚነት ፤ የተማረ የሰው ሃብት እና ሌሎችም መልካም አጋጣሚዎች ያሉ በመሆኑ ጎንደርን ለኢንቨስትመንት ተመራጭ ያደርጋታል፡፡
በአሁኑ ወቅት ከተማችንን ብሎም ክልላችንን በፍጥነት ለማልመትና ለማሳደግ፣ የስራ አጥ ቁጥርን ለመቀነስና ድህነትን ለመቅረፍ የኢንዱስትሪው ክፍለ ኢኮኖሚ የመሪነቱን ሚና ይጫወታል፡፡ ስለሆነም መንግስት አምራች ኢንዱስትሪዎችን ልዩ ትኩረት በመስጠት ከተማችንን ሆነ ክልላችንን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማሳደግ በርብርብ ላይ ይገኛል፡፡ በሃገራችን ለረጅም ጊዜ ተንሰራፍቶ የቆየዉን ስር የሰደደ ድህነትን በማስወገድ በምትኩ ለዜጎቻችን የተሻለ የገቢ ምንጮችን በመፍጠር የኑሮ ደረጃቸዉን በማሻሻል በአለም ላይ ከሚገኙ መካከለኛ ገቢ ካላቸዉ የአለም አገራት ተርታ ለማሰለፍና በከተሞች ድህነትን ለመቀነስና የነዋሪዉን የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻል በዋናነት ከተዘረጉት ስትራቴጂዎች ዉስጥ የኢንዱስትሪው ክፍለ ኢኮኖሚ የመጀመሪያዉን ስፍራ እንደሚይዝ ይታወቃል፡፡
የጎንደር ከተማ አስተዳደር በ2022 ዓ/ም በአምራች ኢንዱስትሪና በቱሪዝም በኢትዮጵያ ቀዳሚ ተወዳዳሪና ተመራጭየኢንቨስትመንት መዳረሻ ሆኖ ማየት ነው፡፡
- በአገር አቀፍ፣ ክልላዊና ከተማ አስተዳደራዊ ሁኔታዎች እና አዝማሚያዎች ጋር በማጣጣም የዘርፉን ማነቆዎች በመለየት እና የመፍትሄ አቅጣጫዎችን በማመላከት በክልሉ ለግሉ ክፍለ ኢኮኖሚ ሳቢ እና ምቹ ሁኔታዎች እንዲፈጠሩ ማድረግ፤
- አገር አቀፍ፤ ክልላዊና ከተማ አስተዳደራዊ ተሞክሮዎች ላይ ተመስርቶ የኢንቨስትመንት አማራጮችን በማስፋትና ለባለሃብቱ ወሳኝ የሆኑ መረጃዎችን በማደራጀት፣ አስቀድሞ በመዘጋጀት፣ ውጤታማ የፕሮሞሽን ሥራ በማከናወን የኢንቨስትመንት ፍሰትን ማሳደግ፤
- የከተማ አስተዳደሩን ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት አገልግሎት አሰጣጥን ተገልጋይ ተኮር በማድረግ፣ የአገልጋዩን አቅም በመገንባትና በቴክኖሎጂ በመደገፍ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቅ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በመስጠት የኢንቨስትመንት ውጤታማነትን እና ዘላቂነትን በማረጋገጥ የከተማውን ኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር ማፋጠን፤
- ገቢ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በማምረት የሚተኩ ማኑፋክቸሪንግ እና ሌሎች አምራች ኢንዱስትሪዎችን በክልሉ ማስፋፋት፤
- ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶችን የሚያመርቱ የማኑፋክቸሪንግ፣ የግብርና እና ሌሎች አምራች ኢንዱስትሪዎችን ማስፋፋትና ተወዳዳሪነታቸውን ማጎልበት፤
- በቱሪዝምና በሌሎች አስቻይ የአገልግሎት ዘርፎች የግሉ ኢንቨስትመንት እንዲስፋፋ እና ተጠናክሮ ለኢኮኖሚው ጉልህ አስተዋጽኦ የሚያደርግበትን ሁኔታ ማመቻቸት፤
- በኢንቨስትመንት የተሰማሩ የግል ባለሀብቶችን ደግፎ ውጤታማ በማድረግ ኢንቨስትመንትታቸውን እንዲያስፋፉ፣ እንዲያስተሳስሩ እና ጥራት ያለው የስራ እድል እንዲፈጥሩ የሚያስችሉ ድጋፎችን ማድረግ፤
- የላቀ አገልግሎት፤
- ዘመናዊነት፤
- የተገልጋይ ርካታ፤ ዝግጁነት፤
- ቅንጅታዊ አሰራር፤
ዜናዎች
አገልግሎቶች
የኢንቨስትመንት ፍቃድ መስጠት
የኢንቨስትመንት ማስፋፊያና እድሳት
የኢንቨስተመንት ፈቃድ ምትክ፣ ለውጥ፣ ዝውውርና ማስተላለፍ
የኢንቨስትመንት ፍቃድ ስረዛ
አሃዞች
የጎንደር ከተማ አጠቃላይ ገጽታ
- ጎንደር ከተማ ከዛሬ 379 ዓመት በፊት ተቆረቆረች፡፡
- ለ250 ዓመታት የኢትዮጵያ መናገሻ ከተማ ሆና ቆይታለች፡፡
- የቆዳ ስፋት 31,000 ሄ/ር ነው፡፡
- ክ800,000 በላይ ህዝብ ያላት (በ6 ክፍለ ከተሞች፤በ25 የከተማ ቀበሌ እና በ11 የገጠር ቀበሌዎችን ጨምሮ) በክልላችን ካሉሜትሮ ፖሊታን ከተሞች አንዷ ናት ፡፡
- የንግድ ማዕከል መአከል ከተማ በመሆነዋ በዞኑ የሚከናወኑትን የልማት ስራዎች ማከናወኛ ዋና ማዕከል ናት፡፡
- ጅኦግራፊያዊ አቀማመጥ በ12 0 37 15’ ሰሜን እና በ120 400 15 ሰሜናዊ ኬክሮስ ሀሳብ መስመር እንዲሁም በ370 ምዕራብ እና በ370 32‹00ምዕራባዊ የኬንትሮስ የሀሳብ መስመር ላይ የምትገኝ ሲሆን ከባሀር ጠለል በላይ ያላት ከፍታ ደግሞ ከ2000-2200 ሜትር ላይ ትገኛለች፡፡
- የአየር ንብረት ወይና ደጋማ ሲሆን ዓመታዊ የዝናብ መጠኑ እስከ 18ዐዐ ሚ.ሜትር ሲደርስ አማካይ የሙቀት መጠኑም 2ዐ0 ዲግሪ ሴልሺየስ ይደርሳል
- ከአዲስ አበባ ያላት ርቀት 748 ኪ.ሜ ሲሆን ከባህር ዳር 182 እንዲሁም ከሱዳን 220 ኪሜ ርቀት ትገኛለች፡፡
ምቹ ሁኔታዎች
የመሬት አቅርቦት
ለማንፋክቸሪንግ አና በአግሮ ፕሮሰሲንግ ለሚሰማራ ባለሀብት ቦታ በምደባና በዝቅተኛ የሊዝ ዋጋ ይሰጣል፣ ለሆቴሎችና ሌሎች ዘርፎች በጫራታ እየተሰጠ ያለበት ከተማ ነው ጎንደር፡፡
መሰረተ ልማት
በከተማችንም ሆነ በኢንዱስትሪ መንደር በተሻለ መልኩ የተሟላ መሰረተ ልማት አለ ማለት ይቻላል (ከመንገድ ፣ ፣ከውሃ አቅርቦት ፣ የአየር እና የየብስ ትራንስፖርት፣ ደረቅ ወደብ ተጠቃሚነት የመሳሰሉት አገልግሎቶች ስኬታማ ናቸው በከተማችን፡፡
የሰው ሃይል
በከተማችን ሰፊ እና የተማረ የሰው ሀይል በመኖሩ በተመጣጣኝ ክፍያ በቂ ሰራተኛ ማግኘት የሚቻልበት ከተማነው ጎንደር ፡፡
ማበረታቻዎች
በከተማችን ባሉየፋይናንስ ተቋማት አማካኝነት ባለሀብቱ ብደር እያገኘ ነው፡፡ በተለይ ልማት ባንክ አፈጻፀሙ እንዲፀነክር ጥረት የሚያስፈልገው ቢሆንም ሁለት ዓይነት የብድር አቅርቦት እየሰጠ ነው፡፡
የኢንዱስትሪ ግብዓቶች
በአካባቢው ለኢንዱስትሪው ግባት ሊሆን የሚችል የእንስሳትና የሰብል ውጤቶች በሰፊው መገኘቱ /ሰሊጥ፣ ጥጥ፣የመሳሰሉት/
የገበያ ትስስር
በቅርብ እረቀት ባሉት ከሱዳን ጋር 220ኪ/ሜ፣ ከኤርትራ በ255ኬ/ሜ የደረቅ ወደብ የገበያ ትስስር ማድረግ መቻሉ፡፡የቱሪስት መስዕህብ ያሉባት ከተማ ከመሆኗ ጋር ተያይዞ ጥሩ የገበያ ዕድል ያላት ከተማ መሆኗ ሌሎችም መልካም አጋጣሚወች ያሉ በመሆኑ ጎንደርን ተመራጭ ከተማ ያደርጋታል ፡፡
የኢንቨስትመንት አማራጮች በማኑፋክቸሪንግ ፤ ማህበራዊ እና አገልግሎት ዘርፎች
የአግሮ ፕሮሰሲንግ ምግብ እና ፋርማሲቲካል
ቆዳና ጨርቃ ጨርቅ
ትምህርትና ጤና
ኮንስትራክሽን ግብዓትና ኬሚካል
ሆቴልና ቱሪዝም
የእንጨትና ብረታ ብረት
ቅይጥ ንግድ
አጋር አካላት
አድራሻ
- ፋሲል ክፍለ ከተማ፣ ጎንደር፣ ኢትዮጵያ
- +251 58 111 0904 / +251 918 7776 09
- Fax: +251 58 111 0904
- investment@cityofgondar.com