የኢንቨስትመንት ማስፋፊያ እና ኢንዱስ/ዞን ልማት
- ወ/ሮ የዝና ተፈራ
- የኢንቨስትመንት ማስፋፊያ እና ኢንዱስ/ዞን ልማት ቡድን
- +251 918 71 1013
- yezena@cityofgondar.com
በኢንቨስትመንት ማስፋፊያ ኢንዱስትሪ ዞን ልማት ቡድን የሚሰጡ የዓገልግሎት አይነቶች
የኢንቨስትመንት የማስፋፊ ሥራዎችን መስራት
- በጎንደርከተማ እና ዙሪያው ኢንቨስት ለማድረግ ያሉ ምቹ ሁኔታዎችንና የኢንቨስመንት አማራጮች በማስተዋወቂያ ስልቶች መያዝ እና ማስተዋወቅ፣
- በዘርፉ የተሰማሩትን የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች የሚገጥሟቸውን ችግሮችና መንስኤዎች ማጥናት፣
- አዳዲስ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶችን ወደ ዞኑ ለመሳብ የኢንቨስትመንት ፕሮሞሽን መረጃዎች ተደራሽ ማድረግ፡፡
- አዳዲስ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክት ፕሮፋይሎችን ማዘጋጀት/እንዲዘጋጁ ማድረግና ትኩረት በተሰጣቸው የኢንቨስትመንት መስኮች ላይ ያነጣጠረ የኢንቨስትመንት ፕሮሞሽን በመስራት ኢንቨስትመንትን ማሳደግ/ማስፋፋት
- በራስ አቅም፤ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማትና አማካሪ የሚጠኑ የፕሮጀክት ሃሳቦችን ለይቶ ከሚመለከተው አካል ጋር በመተባበር እና እንዲጠኑ በማድረግ የኢንቨስትመንት ፕሮሞሽን የአሠራር ሂደትና የገጽታ ግንባታ የሚሻሻልበትን ስልት እንዲቀየስ ያደርጋል፣
- የባለሀብቶችንና የኢንቨስትመንት አስፈጻሚ አካላት የአቅም ግንባታ ስልጠናና ቅንጅታዊ አሰራር መፍጠር
- ባለሃብቶች ወደ ተለያዩ ኢንቨስትመንቶች እንደሰማሩ መሳብ፣ መደገፍና መከታተል፣
- በኢንቨስትመንት ማስፋፋት ዙሪያ የአቅም ግንባታ ሥልጠና መስጠት፣
የኢንቨስትመንት አዲስ፣ ትክ፣ ለውጥ ፈቃድ መስጠት፣ ማደስ፣ መሰረዝ፣
- በኢንቨስትመንት ህጉ መሰረት የተሞላው ማመልከቻና አባሪ መረጃዎች ትክክል መሆናቸውን በማረጋገጥና ቅድመ-ሁኔታውን አሟልተው ሲገኙ ለሀገር ውስጥ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ይሰጣል፣ ያድሳል፣ ይተካል፣ ያሻሽላል፣ ያግዳል፣ ይሰርዛል፤
- ለመ/ቤቱ በተሰጠው ውክልና መሰረት የኢንቨስትመንት ፈቃድ ለተሰጣቸው ባለሃብቶች የንግድ ስራ ፈቃድ ጥያቄን መርምሮ የውሳኔ ሃሳብ ያቀርባል፣ቅድመ-ሁኔታውን አሟልተው ሲገኙ የንግድ ስራ ፈቃድ ይሰጣል፣ያድሳል፤ያግዳል፤ምትክ ይሰጣል፤ይሰርዛል፤
- ለመ/ቤት በተሰጠው ውክልና መሰረት አዲስ ለሚመሰረቱ ድርጅቶች የመመስረቻ ፅሁፍና የመተዳደሪያ ደንብ ያዋውላል፣
- በኢንቨስትመንት ፈቃድ አሰጣጥና በንግድ ስራ ፈቃድ አሰጣጥ ላይ አስፈላጊ የሆነውን ማብራሪያና ምክር ይሰጣል፣
- በፈቃድ እድሳትና በንግድ ስራ ፈቃድ አሰጣጥና ሂደት የሚነሱ አቤቱታዎችንና ቅሬታዎችን በተመለከተ አግባብነት ካላቸውና ውክልና ከሰጡ መ/ቤቶች በቅርብ እየተገናኘ በመወያየት ለውሳኔ የሚያመች የመፍትሄ ሃሳቦችን አዘጋጅቶ ያቀርባል፣
- የንግድ ማህበራት የስም ስያሜ አሰጣጥ ላይ የሚነሱ አቤቱታዎችን በተመለከ
- በንግድ ህጉ መሰረት መርምሮ የውሳኔ ሃሳብ ያቀርባል፣
- ከውክልና ሰጭ መ/ቤቶችና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር የዋና ንግድ ምዝገባ በሚቀርበው ጥያቄ መሰረት የሚከናወንበት ሁኔታ ያመቻቻል፣
- ለሚሰጡ የፈቃድና የምዝገባ አገልግሎቶች አስፈላጊውን ክፍያ ያስፈጸማል፤
- እንዲሰረዙ የተለዩ የኢንቨስተመንት ፈቃድ መረጃዎችን በየወቅቱ በመለየት ወቅታዊ ማድረግ /መሰረዝ/
- ስለተከናወኑ የፈቃድና ምዝገባ አገልግሎቶች የተሟላና ወቅታዊ መረጃዎችን በሀርድና በሶፍት ኮፒ አደራጅቶ ይይዛል፣ ያሠራጫል ፤
- መረጃዎችን በሀርድና በሶፍት ኮፒ አደራጅቶ መያዝና ለሚመለከተው አካል መስጠት፣
- አዲስ የተሰጡ የኢንቨስትመንት ፈቃዶችን መረጃ በመጣራት ለዳታቤዝ ግብዓት ማዘጋጀት፣፣
የኢንዱስትሪ ዞን ልማት
- ዓለም አቀፍ ስታንዳርዱን ያሟላና ለልማት ዝግጁ የሆነ የኢንዱስትሪ ዞን ጥናት ማካሄድ፤
- በክላስተር ለሚዘጋጁ የኢንዱስትሪ ዞን የፕሮጀክት ፕሮፋይል ሰነድ ማዘጋጀት፤
- የኢንዱስትሪ ዞኖች ፕሮፋይል ሰነድ አዋጭነትን መገምገም ፤መከታተል፤
- አልሚ ባለሃብቶችንና አምራች ባለሃብቶችን ለመሳብ የፕሮሞሽን ስራዎችን መስራት፤
- ለአልሚ ባለሃብቶች የተላለፈውን የማምረቻ ቦታ በትክክል ስራ ላይ መዋሉን መገምገምና የመከታተል ስራ መስራት፤
- ፕሮጀክቶች መሰረተ ልማት( መንገድ፣ መብራት፣ ብድር፣ ውሃ) እንዲሟላላቸው ድጋፍ ማድረግ፣
- ፕሮጀክቶች ከቀረጥ ነፃ ማበረታቻና የግብር እፎይታ እንዲያደኙ ድጋፍ ማድረግ፣
- በውላቸው መሠረት የወሰዱትን መሬት ትግበራ ላይ ካላዋሉ አስፈላጊውን ክትትል በማድረግ በሬቱን ወደ መንግስት ተመላሽ እንዲሆንና እርምጃ እንዲወሰድባቸው የውሳኔ ሃሳብ ማቅረብና ተፈፃሚነቱን መከታል
- የኢንቨስትመንት ፕሮጀቶች ክትትልና ድጋፍ መሬት እንዲያገኙ ለከንቲባ እና ለሚመለከተው አካል መላክ
- የፕሮጀክቶችን ፕሮፖዛል አዋጭነትን መገምገም እና መከታተል፤
- ለኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ክትትልና ድጋፍ በማካሄድ ወደ አፈፃፀም ማስገባት፣
- የኢንቨስትመንት ፕሮጀክት መረጃዎችን መተንተን ፤
- የአቅም ግንባታ እና የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና መስጠት፣
- በመንግስት የተሰጡ የኢንቨስትመንት መብቶች በአግባቡ ስራ ላይ ስለመዋላቸው መከታተልና ማረጋገጥ፣
የኢንቨስትመንት ፕሮጀቶች ክትትልና ድጋፍ አገልግሎት መስጠት
- ውጤት-1፡- የስራ ድርሻዉን ማቀድ፤መፈፀም፤ማደራጀት እና ሪፖርት ማቅረብ
- ውጤት-2 የፕሮጀክቶችን ፕሮፖዛል አዋጭነትን መገምገም እና መከታተል፤
- ውጤት-3፡-ለኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ክትትልና ድጋፍ በማካሄድ ወደ አፈፃፀም ማስገባት፣፤
- ውጤት 4 ፡ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክት መረጃዎችን መተንተን ፤
- ውጤት 5፡ የአቅም ግንባታ እና የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና መስጠት፣
- ውጤት 6 ፡በመንግስት የተሰጡ የኢንቨስትመንት መብቶች በአግባቡ ስራ ላይ ስለመዋላቸው መከታተልና ማረጋገጥ፣
- ፕሮጀክቶች ከቀረጥ ነፃ ማበረታቻ እንዲያደኙ ድጋፍ ማድረግ፣
- ፕሮጀክቶች መሰረተ ልማት( መንገድ፣ መብራት፣ ብድር፣ ውሃ) እንዲሟላላቸው ድጋፍ ማድረግ፣
- በውላቸው መሠረት የወሰዱትን መሬት ትግበራ ላይ ካላዋሉ አስፈላጊውን ክትትል በማድረግ በሬቱን ወደ መንግስት ተመላሽ እንዲሆንና እርምጃ እንዲወሰድባቸው የውሳኔ ሃሳብ ማቅረብና ተፈፃሚነቱን መከታል
ኑ እና ጐንደርን እናልማ
የጐንደር ከተማ አስተዳደር ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ
አድራሻ
- ፋሲል ክፍለ ከተማ፣ ጎንደር፣ ኢትዮጵያ
- +251 58 111 0904 / +251 918 7776 09
- Fax: +251 58 111 0904
- investment@cityofgondar.com